ጽዮን ኾይ ንጉሥሽ ለጠላት አይሸነፍም፤ አገርንም አይተዋትም

ጥንተ ነገሩ ለታቦት/ጽላት

ታቦት ትርጉሙማደሪያሲኾንመገለጫምይኾናል፡፡ የተዠመረው ከብሉይ ኪዳን ነው፡፡ ታቦትን ለመዠመሪያ ጊዜ ጠርቦ አበጅቶ የሠራ ንጉሠ ፳ኤል እግዚአብሔር ነበር፡፡ ዘፀ. ፴፩፥፲፰እግዚአብሔርም ከሙሴ ጋር በሲና ተራራ የተናገረውን በፈጸመ ጊዜ በእግዚአብሔር እጅ የተጻፈባቸው ጽላት ሰጠውዘፀ. ፴፪፥፲፭፲፯ሙሴም ሁለቱን የምስክር ጽላት በእጁ ይዞ ከተራራው ወረደ፤ ጽላቱም የእግዚአብሔር ሥራ ነበሩ፤ይለናል፡፡

ታቦትና ጽላት በሐዲስ ኪዳን

ታቦተ ሕጉ የተሠራው በብሉይ ኪዳን ብቻ እንዲያገለግል ሳይኾን እስከዘለዓለም ድረስ እግዚአብሔር ያሰበለት ግዳጅ፣ ተለእኮ ስላለው ነው፡፡ ንጉሡ ሰሎሞን ታላቁን ቤተ መቅደስ ከሠራ በኋላ ፩ኛነገ. ፰፥፩፷፮ እንደጨረሰ ወደእግዚአብሔር ጸለየ፤ እግዚአብሔርም ለዘለዓለም የሚኖርበት ማደሪያ ቤት እንደሠራለት፣ የእግዚአብሔር ዐይኖች በቤተመቅደሱ እንዲኾኑ፣ ስሙም በቤተመቅደሱ እንዲመሰገን፣ ሕዝቡ ኹሉ በዚህ ቤተመቅደስ የሚጸልዩትን ጸሎት እንዲቀበል ተመኘ፡፡ 

ወዲያውኑ እግዚአብሔርም በጐ ምላሽ ለሰሎሞን መለሰለትእግዚአብሔርም አለው፡ - በፊቴ የጸለይኸውን ጸሎትህንና ልመናህን ሰምቻለሁ፤ ለዘለዓለምም ስሜ በዚያ ያድር ዘንድ ይህን የሠራኸውን ቤት ቀድሻለሁ፤ ዐይኖቼና ልቤ በዘመኑ ኹሉ በዚያ ይኾናሉአለ ፩ኛ ነገ. ፱፥፫፡፡ እግዚአብሔርን ንጉሡን ሰሎሞንን ታቦተ ጽዮንን ለማሳረፍ ስለሠራው በጐ ሥራ የዳዊትን አይነት ምርቃት መረቀውእኔ ከ፳ኤል ዙፋን ከዘርህ ሰው አታጣም ብዬ ለአባትህ ዳዊት እንደተናገርሁ የመንግሥትህን ዙፋን በ፳ኤል ላይ ለዘለዓለም አጸናለሁ 

ታቦትና አገር፣ ታቦትና ጠላት

በአሁን ዘመን የሰሎሞን ቤተ መቅደስም እንዳለ አይታወቅም፤ ታቦተ ሕጉም በ፳ኤል የለም፡፡ ታዲያ እግዚአብሔርለዘለዓለምም ስሜ በዚያ ያድር ዘንድ የሠራኸውን ቀድሻለሁ፤ ዐይኔና ልቤም በዘመኑ ኹሉ በዚያ ይኾናሉሲል የሰጠውን ቃልኪዳን አጠፈ ማለት ነዋ፤ አላጠፈም፡፡ ዓለም ታቦተ ሕጉን ሲተዉ ኢትዮጵያውያን በቤተ መቅደስ ስለሚገለገሉባቸው የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ሕያው ኾኗል፡፡ 

እንዲያውም ታቦተ ጽዮን በኢትዮጵያ የክብር መጠለያ ስለተገኘላት የእግዚአብሔር ዐይኖችና ልቡ በሰሎሞን ቃልኪዳን መሠረት በዚህ ይኾናሉ፤ ለዚህም ነው ኢትዮጵያ ዳሯ እሳት መሃሏ ገነት ኾኖ ለዘመናት ጠላት እየተንበረከከላት የኖረችው፡፡ወቀተለ ነገሥተ ጽኑዓነብርቱዎችንም ነገሥታትን ገደለ እንዳለ ልበ አምላክ ዳዊት መዝ.፩፻፴፭ ታቦተ ጽዮን ሳለቻቸው ፳ኤል ጠላቶችን ኹሉ ድል የሚያደርጉ ነበሩ፡፡ ያለ እርስዋ ግን በጠላቶቻቸው ላይ ወደቁእርስዋም የእግዚአብሔር ታቦት ተማርካለችና ክብር ከ፳ኤል ለቀቀች፤እንዳለ ፩ኛ ሳሙ. ፬፥፲፱፳፪ በምትኩ ታቦተ ጽዮን የከተመችባት ኢትዮጵያ ጠላት የማይደፍራት ኾነች ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያውያን እንዲህ እያሉ ይዘምራሉንጉሥኪ ጽዮን ኢይትመዋዕ ለጸር ወኢየኃድጋ ለሀገርጽዮን ኾይ ንጉሥሽ ለጠላት አይሞትለትም/አይሸነፍም፤ አገርንም አይተውለትም፡፡

ታቦትና ጽላት በሰማይ 

መላእክትና የሰማይ ሠራዊትም ታቦተ ሕጉን በዛሬዋ እለት እየተገለገሉበት እንደሚገኙ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡እነኾም በሰማይ ያለው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተከፈተ በመቅደሱ ውስጥም የቃል ኪዳኑ ታቦት ታየ፡፡ራዕ ፲፩፥፲፱ ፲፭፥፭ ታቦተ ሕጉ ከምድር ኅልፈት በኋላም በሰማይ እንደሚኖር ይህ አብነት ነው፡፡ ስለዚህ ታቦት በብሉይ ኪዳን የነበረ ብቻ ሳይኾን በሐዲስም እስከዘለዓለምም የሚኖር ነው፡፡

ታቦት፣ ዕጣን፣ ንጹሕ ቊርባን

ታቦተ ሕጉ በ፳ኤል ብቻ የነበረና በሐዲስ የማይኖር ቢኾን ኖሮከፀሐይ መውጫ ዠምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ይከበራልና፤ በየስፍራው ለስሜ ዕጣን ያጥናሉ፤ ንጹሕንም ቁርባን ያቀርባሉ፤ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይኾናልና ይላል ኹሉን የሚችል እግዚአብሔርሚል ፩፥፲፩ የሚለው የእግዚአብሔር ቃል ሊታጠፍ ነበር ማለት ነው፡፡ ይህ ትንቢት በቀጥታ ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች መኾኑ ግልጥ ነው፡፡ ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ቤተ መቅደስም ኾነ የዕጣን የቁርባን አገልግሎት እንኳን ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ ላሉ አሕዛብ በኢየሩሳሌም ከሚኖሩ የእግዚአብሔር ሕዝቦች በቀር ለ፳ኤል ጎረቤቶች እንኳ አልተፈቀደምና፡፡ ነቢዩ ሚልክያስ ንጹሕ ዕጣን ያለው በማቴ ፪፥፲፩ እንደተነገረ ከአሕዛብ ወገን የኾኑ ሰብአ ሰገል በቤተልሔም ለክርስቶስ ካቀረቡት ጀምሮ እስከ ዛሬ በዓለም ያለን ክርስቲያኖች በቤተመቅደስ፣ በታቦቱ ዙሪያ በክርስቶስ ስም ለክርስቶስ የምናቀርበው ቅዱስ ዕጣን ነው፡፡

አንድም በማቴ ፳፮፥፳፮ ጌታ ኅብስቱን አንሥቶ ነገ የሚቆረሰው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ወይኑንም አንሥቶ ነገ ስለብዙዎች ኃጢአት የሚፈሰው ደሜ ይህ ነው ብሎ ለሐዋርያት የሰጣቸው የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን በኢየሩሳሌም ብቻ መኾን የሚገባቸው ቤተ መቅደሱ፤ ዕጣኑ፣ ቁርባኑ፣ በክርስቶስ ደም በአዲስ ሕይወት፣ በአዲስ ተፈጥሮ፤ በአዲስ ሥርዓት፣ ክርስቲያኖች ለኾንን ለዓለም ሕዝቦች በየሥፍራው (በያለንበት) እንድንጠቀምባቸው ከተፈቀዱልን በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩት ሁለቱ ጽላት ከፀሐይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ በየቤተ መቅደሳችን ለቊርባኑ የክብር ዙፋንነት እንገለገልበታለን፡፡ 

ታቦት የእግዚአብሔር የክብሩ መግለጫ ዙፋን እንደኾነ ኹሉ ተገቢው ክብር እንዲሰጠው ቅዱስ መጸሐፍ ያዝዛል፡፡ ታቦቱን የተዳፈሩት ፍልስጥኤማውያን ዳጎንን አፈራርሳ እነርሱንም በአባር ቸነፈር እንደመታቻቸውና በክብር የተቀበላትን አቢዳራን ግን ለሦስት ወር ቤቱንና ቤተሰዎቹን እንደባረከችለት መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ ፩ኛ ሳሙ.  
ለታቦት ሊሰጥ የሚገባው ክብር

በ፩ኛሳሙ. ፮፥፲፭፳፫ ዳዊት በታቦተ ጽዮን ፊት በዝማሬ ሲያመሰግን ሜልኮል ደግሞ እርሱ በሰጠው ክብር ስትሳለቅ እንደነበር ይነግረናል፡፡ ከዚህ ቀጥሎ ለዳዊትእስመ እምፍሬ ከርስከ አነብር ዲበ መንበርከከወገብህ ፍሬ በመንበርህ ላይ አኖራለሁ የሚል ታላቅ ቃል ኪዳን ሲሰጠው ሜልኮል ደግሞኢወለደት ሜልኮል እስከአመሞተትሜልኮልም እስከሞተችበት ጊዜ ድረስ አልወለደችም ተባለ፡፡ ይህ ታቦተ ሕጉ የሚያከብሩትን ሰዎች የሚያከብር የሚያዋርዱትን ደግሞ የሚቀሥፍ መኾኑን ያስተምረናል፡፡ 

ታቦት ከመነሻው ከምንጩ ጀምሮ በክብር የኾነ መኾኑን በዘፀ. ፫፥፭ ላይወደዚህ አትቅረብ አንተ የቆምክባት ሥፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን ከእግርህ አውልቅብሎ እግዚአብሔር ሙሴን ሲያዝዘው እናያለን፡፡ በኋላም ለ፳ኤል በኢያሱ ሲናገር ኢያ. ፫፥፫የአምላካችሁ የእግዚአብሔር የቃልኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመው ባያችሁት ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፤ በእናንተና በታቦቱ ያለው ርቀት በስንዝር ሁለት ሺህ ክንድ ያህል ይሁንበማለት ተናግሯል፡፡ 

በአጠቃላይ ታቦተ ሕጉ በሐዲስ ኪዳን በክርስትና በበለጠ ክብርና አክብሮት አገልግሎት እየተፈጸመበት ነው፡፡ ይህም የኾነው የሚሠዋው መሥዋዕት አማናዊው የክርስቶስ ክቡር ደሙ ቅዱስ ሥጋው ስለኾነ ነው፡፡ የበግና የላም፣ የዋኖስና የርግብ ደም የሚፈስበት የብሉይ ኪዳን ታቦተ ሕግ ይህን ያክል ክብር ካለውዝንቱ ውእቱ ደምየ ዘሐዲስ ሥርዓት ዘይትከዐው በእንተ ብዙኃን ለኅድገተ ኃጢአትስለብዙዎች ኃጢአት በሐዲስ ኪዳን የሚፈስሰው የክርስቶስ ደም (ማቴ.፳፮፥፳፰) የሚከብርበት የሐዲስ ኪዳን ታቦተ ሕግማ ምንኛ አብዝቶ ይከብር፡፡ 

እርስዋም የእግዚአብሔር ታቦት ተማርካለችና ክብር ከ፳ኤል ለቀቀች፤፩ኛ ሳሙ. ፬፥፳፪
ይቈየን!

አስተያየቶች